የቅድስት ቤተክርስቲያን የምስጋና መዝሙራት

Holy Church

በደምህ ዋጅተህ

Lyrics

በደምህ ዋጅተህ ያፀናሀትን

ጠብቅልን ቤ/ክርስቲያንን

ጽዮንን ክበቧት ቅጥሮቿንም ዙሩ

ሲል ያመሠገናት ዳዊት በመዝሙሩ /2/

ወልድ ዋህድ ብሎ ጴጥሮስ ሲመሰክር

መሠረት ነህ ብለህ ሰጥተኸዋል ክብር /2/

እመሠርታለሁ ባንተ መሠረት

የሲኦል አበጋዝ አይችሉም ለማጥፋት/2/

የቅዱሳን አገር የአምላክ ማደሪያ

ምዕራገ ጸሎት የሐጢአት ማስተሥረያ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening