ጠቅላላ

General

እግዚአብሔርን ጠራሁት

Lyrics

እግዚአብሔርን ጠራሁት በሀዘኔ ጊዜ

እግዚአብሔርን ጠራሁት በጭንቀቴ ጊዜ

አወጣኝ ከጭንቀት ከሀዘን ከትካዜ /2/

የልመናዬን ድምጽ እርሱ ሰምቷልና

ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሏልና

በዘመኔ ሁሉ ስጠራው እኖራለሁ /2/

ጎስቋላ ብሆንም ምስጋና አቀርባለሁ /2/

እንደ ቃልህ መጓዝ መራመድ አቅቶኝ

የሃጢያት መንገድ ማዕበሉ ገፍቶኝ

ወደ እርሱ ስማጸን ደግሞ ስጸጸት /2/

አላሳፈረኝም መጣ በምህረት /2/

ኖህን እንዳዳንከው እኛንም አድነን

ከቀስቱ እንድናመልጥ ምልክትን ስጠን

በትርህ ምርኩዝህ እነሱ ያጽናኑኝ /2/

አንተ ከኔ ጋር ነህ አልፈራም ክፉውን /2/

በበዛ ምህረቱ ያለፈውን ትቶ

በፍቅሩ ጎበኘኝ አልተወኝም ከቶ

ሊቀበለኝ ወዶ ፊቱን አበራልኝ /2/

ማን ይቃወመኛል እግዚአብሔር ካለልኝ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening