ጠቅላላ

General

የስሙ ትርጓሜ

Lyrics

የስሙ ትርጓሜ ማን እንደ እግዚአብሔር ነው

የሰውን ወደ አምላክ የአምላክን ወደ ሰው

እኛን የሚረዳን ዘወትር በምልጃው

የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነው

ከጉድጓድ ተጥሎ ፍጹም ከሚያስፈራው

ከተራቡ አናብስት ዳንኤልን ያዳንከው

እኛንም ተራዳን ቸል አትበለን

ሰይጣን በተንኮሉ ወጥመድ ሳይጥለን

የክፉ ሰው ስራው ክፉ ሐሳብ ነውና

በቅንነት መንገድ ከቶ አይሄድምና

የሞቱን ደብዳቤ ለባህራን ሲሰጠው

ሚካኤል አጥፍቶ በደስታ ለወጠው

ገና ብላቴና ሳለሁ አንድ ፍሬ

ሰው ሁሉ ሲንቀኝ ምስጋናን ጀምሬ

ጸጋዬን አብዝቶ ያበቃኝ ለዚህ ክብር

የሚካኤል አምላክ ይመስገን እግዚአብሔር

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening