✦
ጠቅላላ
•General
የስሙ ትርጓሜ
Lyrics
የስሙ ትርጓሜ ማን እንደ እግዚአብሔር ነው
የሰውን ወደ አምላክ የአምላክን ወደ ሰው
እኛን የሚረዳን ዘወትር በምልጃው
የመላዕክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነው
ከጉድጓድ ተጥሎ ፍጹም ከሚያስፈራው
ከተራቡ አናብስት ዳንኤልን ያዳንከው
እኛንም ተራዳን ቸል አትበለን
ሰይጣን በተንኮሉ ወጥመድ ሳይጥለን
የክፉ ሰው ስራው ክፉ ሐሳብ ነውና
በቅንነት መንገድ ከቶ አይሄድምና
የሞቱን ደብዳቤ ለባህራን ሲሰጠው
ሚካኤል አጥፍቶ በደስታ ለወጠው
ገና ብላቴና ሳለሁ አንድ ፍሬ
ሰው ሁሉ ሲንቀኝ ምስጋናን ጀምሬ
ጸጋዬን አብዝቶ ያበቃኝ ለዚህ ክብር
የሚካኤል አምላክ ይመስገን እግዚአብሔር
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.