ጠቅላላ

General

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን

Lyrics

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ በመስቀል ላይ ሆነህ አባት ሆይ

ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ

የሰማይ ከዋክብት በሙሉ ረገፉ

ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ

ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ

ስጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ

ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ

አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ

ማርና ወተት ለሚመግበው

ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው

አካሉ ሲወጋ ውሃ ደም ፈሰሰ

በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ

የእስራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ

ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክ

እናትህ ስታለቅስ በመስቀል ስር ሆና

ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያጽናና

መላዕክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ

የአይሁድ ሰራዊት ፈርተው ተረበሹ

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening