ጠቅላላ

General

የጸጸት እሮሮ

Lyrics

አምላክ ሆይ ወደ እኛ ባትመጣ /2/

ለብሰህ የማርያምን ስጋ /2/

ባክኖ የነበረው የአዳም ዘር /2/

ውጤቱ ነበር የሚያሰጋ /2/

በዚያ ዓመት በዚያች ወር በዚያች ቀን /2/

ድህነትን ለሰው ልጅ ስትሰጥ /2/

ምን የበዛ ነበር ትህትና /2/

ትዕግስትህ የማይለወጥ /2/

የአሾህ አክሊል ደፍተህ /2/

በራስህ ጎንህን ሲወጉ በጦር /2/

አንተ ግን ለእነርሱ ከአባትህ /2/

ምህረትን ትለምን ነበር /2/

ግን መቼ አወቁህ እነርሱ /2/

በሃጢያት ደንድኖ ልባቸው /2/

መድሃኒታቸውን ገረፉት ሰቀሉት /2/

አንተም ሞትክላቸው /2/

በዚያች በደብረ ዘይት ቦታ /2/

ደስታና ለቅሶ ሲፈልቅ /2/

ከቶ ከየት ይሆን እጣዬ /2/

ያን ጊዜ የእኔ አወዳደቅ /2/

የጸጸት እሮሮ በፊትህ /2/

እንዳያቃጥለኝ እኔን /2/

እርዳኝ ፈጣሪዬ እኔን /2/

አድሰው የዛገው ልቤን /2/

ዳግም ስትመጣ ለፍርድ /2/

ከዓለም ፍፃሜ በኃላ /2/

ኸረ እንዴት እድለኞች ናቸው /2/

በፊትህ የሚያገኙት ተድላ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening