ጠቅላላ

General

እስመ ለዓለም

Lyrics

እስመ ለዓለም ምህረቱ /2/

አያልቅም ብዙ ነው የአምላክ ቸርነቱ /2/

አመስግኑ ጌታን ሁላችሁ በአንድነት /2/

መሀሪ ነውና ለሰው ልጆች ሕይወት

የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው /2/

ከገሃነም እሳት እኛን ሊያድን ነው

ከማርያም የነሳው ያ ቅዱስ ስጋው

ቀራንዮ ሲውል የሚያሳዝን ነው

ለፈጠረው ፍጥረት እጅግ ተሰቃይቶ

ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ለይቶ

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening