ጠቅላላ

General

ተክለሐይማኖት ፀሐይ

Lyrics

ተክለሐይማኖት ፀሐይ የኢትዮጵያ ሲሳይ

ምዕራፈ ቅዱሳን /2/ በነፍስም በሥጋ አትርሳን

የቅዱሳን እርስት የኢትዮጵያው ብርሃን

የጸሎት ባለቤት የነዳያን መድህን

ገና ሳትወለድ አምላክ የመረጠህ

የድውያን ህመም ፈዋሹ አንተ ነህ /2/

ገና በሶስት ቀን በህፃንነትህ

ጌታን አወደሰው ቅዱስ አንደበትህ

ቀድሞም እግዚአብሔር አስቦሃልና

በወጣትነትህ ወጣህ ለምነና /2/

ሌትና ቀን ሳትመርጥ ክረምትና በጋ

ስትፀልይ ውለህ ስትፀልይ አነጋህ

በመቆምህ ምክንያት አንድ እግርህ ቢነሳ

ጸሎትህን ፈጸምክ ለስጋህ ሳትሳሳ /2/

ምንኛ ድንቅ ነው ቅዱስ ያንተ ብርታት

ሰባት ዓመት ሙሉ በአንድ እግርህ ጸሎት

የዓለም ግሳንግሱ ሀብቱ ሳይስብህ

ለኢትዮጵያ ፀለይክ ቆመህ በአንድ እግርህ /2/

የሐይማኖት ተክል የኢትዮጵያ አባት

ምህረትን ከአምላክህ ለሀገርህ አሰጣት

እኛንም አግዘን ጽድቅን እንድንሰራ

በተሰጠህ ስልጣን ጠብቀን አደራ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening