✦
ጠቅላላ
•General
ወይቤሎሙ ሐሩ
Lyrics
ወይቤሎሙ ሐሩ ወመሐሩ ለዘየአምን /2/
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /4/
በሕይወታችሁ ስበኩ በኑሮአችሁ
ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በዓለም ዙሪያ አዳርሱ ሳትሰለቹ
ደመና ጠቅሳችሁ እንደወፍ
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /2/
በሃጢያት ገመድ ተይዞ ለታሰረው
በዓለም ጽልመት ለተዋጠው
የእውነቱ መንገድ ብርሃኑ ለጠፋበት
በሁለንተናው ፈንጥቁበት
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /2/
የጽድቅ እንጀራ በማጣት ለተራበው
የሕይወትን ውሃ ለተጠማው
ቀቢጸ ተስፋ በልቡ ላደረበት
የወንጌልን ማዕድ አቅርቡለት
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /2/
አይንተ ወንጌል ካህናት ሊቃውንት
ለተልዕኮ የጠራችሁ
ከእውነተኛው ምንጭ ከጌታ ከባህሩ
የሕይወትን ውሃ የጠጣችሁ
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /2/
ሁለንተናችሁ ይነበብ ፊደል ይሁን
በትዕዛዙ ሔዳችሁ
ስራችሁ ይብራ በዓለም እንደ ሻማ
በሕይወታችሁ ሰብካችሁ
ወንጌለ መንግስተ ሰማያት /2/
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.