ጠቅላላ

General

ስምሽን ጠርቼ

Lyrics

ስምሽን ጠርቼ መቼ አፍራለሁ

ማርያም ብዬ መቼ እወድቃለሁ

የምጽናናበት ስምሽ ነውና

ድንግል ሆይ ላቅርብ ላንቺ ምስጋና

ጨለማ ውጦኝ በጠላት ሀገር

ለዘመናትም ስረገጥ ስኖር

ዲያብሎስ ማርኮ ሲያሰቃየኝ

የዓለሙን መድን ወለድሽልኝ

ከአባቶቼ ርስት ከሀገር ወጥቼ

በአህዛብ ሀገር ስኖር ተሽጬ

ደርሰሽ አጽናንተሽ አከበርሽኝ

ብቸኝነቴን አስረሳሽኝ

ድንኳኑ ሞልቶ ሰዉ ታድሞ

አስተናባሪው በጭንቀት ቆሞ

ምን አቀርባለሁ ብዬ ስቸገር

ምልጃሽ ደርሶልኝ ዳንኩኝ ከማፈር

ያሰብኩት ሀሳብ ደመና ሆኖ

ቢበተንብኝ እንደ ጉም ተኖ

ይሆናል ያልኩት ሳይሆን ቢቀርም

በእመ አምላክ እኔስ ተስፋ አልቆርጥም

እናት አባቴ ባያስታውሱኝ

ይህቺ ዓለም ንቃ ገፍታ ብትተወኝ

አንቺ ካለሽኝ ምን እሆናለሁ

አውሎ ነፋሱን ባህሩን አልፋለሁ

ጠላቴ ደርሶ ቢያንገላታኝም

መከራ አብዝቶ ቢያስጨንቀኝም

አላቋርጥም ያንቺን ምስጋና

ውለታሽ ድንግል አለብኝና

ክፉዎች ደርሰው ቢዝቱብኝም

አንቺን መውደዴን አያስተዉኝም

በአህዛብ መሃል ስምሽን ስጠራ

መከታ ሁኚኝ እናቴ አደራ

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening