ጠቅላላ

General

ሌላ ምስጋና

Lyrics

እመቤቴ ሆይ ሀብቴ ነሽና

ሳመሰግንሽ ዲያቢሎስ ቢቀና

ገና አለኝ ገና አዲስ ምስጋና

ገና አለኝ ላንቺ አዲስ ምስጋና

ድልድይ ሆነሽን ተሻግረናል እኛ

አንወሰድም አንሞትም ዳግመኛ

እናት አለችን በላይ በሰማይ

አማላጃችን እሙ ለአዶናይ

ግዮን ከቦታል የርስትሽን ሀገር

ጣፋጭ ተአምርሽ ይኖራል ሲነገር

ዋሻው ያበራል ሜዳው ሳር ቅጠሉ

መለኮሳቱ ንኢ ንኢ ሲሉ

ተፍገመገመ ራደ ጠላታችን

የልጅሽ ሞገስ ሰፍኖ በላያችን

ሞገዱም ይጩህ ዲያቢሎስም ያውራ

ከእሳቱ አንወድቅም ሳለን ካንቺ ጋራ

ቤትሽ አድገናል በአማረው እልፍኝሽ

የንጉሱ እናት እመ ብዙሃን ነሽ

የራማው መላዕክት ክንፎቹን ዘርግቷል

ወደ ገሊላ ምስጋና ተሰምቷል

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening