ጠቅላላ

General

ኦ ሥሉስ ቅዱስ

Lyrics

ኦ ሥሉስ ቅዱስ ተመስገን /2/

ዓለማትን የፈጠርክ እግዚአብሔር ተመስገን /2/

አዳም ሳይፈጠር በዙፋንህ ነበርክ

በአንድነት ሦስትነት እየተመሰገንክ

መላዕክትን ፈጠርክ ስምህን ሊጠሩ

በምስጋና ጸንተው ካነተ ጋር ሊኖሩ /2/

የሰውን ልጅ ፈጠርክ ክብርህን እንዲወርስ

አንተን በማመስገን ሕይወቱ እንዲቀደስ

እኛም ልንጠራህ ባይገባን እንኳን

ለምስጋና ቆመን ደጅህን አንኳኳን /2/

የዓለም ሁሉ ንጉስ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ

ፍጥረትን በሙሉ አውሎ አሳዳሪ

ስላሴን ላወድስ ስሉስ ቅዱስ ልበል

በዓለም ከመክበር በቤታችሁ ልጣል /2/

ዮርዳኖስን ልሁን ሥላሴን ልያቸው

በአንድነት ሦስትነት ቅዱስ ልበላቸው

ትባረክ ትቀደስ ነፍሴ በስላሴ

በአባቶቼ አምላክ በአብርሃም በሙሴ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening