✦
ጠቅላላ
•General
ኦ ሥሉስ ቅዱስ
Lyrics
ኦ ሥሉስ ቅዱስ ተመስገን /2/
ዓለማትን የፈጠርክ እግዚአብሔር ተመስገን /2/
አዳም ሳይፈጠር በዙፋንህ ነበርክ
በአንድነት ሦስትነት እየተመሰገንክ
መላዕክትን ፈጠርክ ስምህን ሊጠሩ
በምስጋና ጸንተው ካነተ ጋር ሊኖሩ /2/
የሰውን ልጅ ፈጠርክ ክብርህን እንዲወርስ
አንተን በማመስገን ሕይወቱ እንዲቀደስ
እኛም ልንጠራህ ባይገባን እንኳን
ለምስጋና ቆመን ደጅህን አንኳኳን /2/
የዓለም ሁሉ ንጉስ የዓለም ሁሉ ፈጣሪ
ፍጥረትን በሙሉ አውሎ አሳዳሪ
ስላሴን ላወድስ ስሉስ ቅዱስ ልበል
በዓለም ከመክበር በቤታችሁ ልጣል /2/
ዮርዳኖስን ልሁን ሥላሴን ልያቸው
በአንድነት ሦስትነት ቅዱስ ልበላቸው
ትባረክ ትቀደስ ነፍሴ በስላሴ
በአባቶቼ አምላክ በአብርሃም በሙሴ /2/
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.