ጠቅላላ

General

ያዕቆብ ከቤርሳቤት

Lyrics

ያዕቆብ ከቤርሳቤት ወደ ካራን ሲሄድ

የለውም ነበረ አማካሪ ዘመድ

ፀሐይ ጠልቃ ነበር ከዛ እንደ ደረሰ

ከእርሱም በታች ድንጋይ ተንተራሰ

ህልምንም ዓለመ ታላቁን ራዕይ

መሰላል ተተክሎ ከምድር እስከ ሰማይ

ሲወጡ ሲወርዱ መላዕክት በእርሱ ላይ

እግዚአብሔርም ቆሞ ከላይ ከጫፏ ላይ

የአባቶችህ አምላክ እኔ እግዚአብሔር ነኝ

ይህን ምድር ለርስትህ እሰጥሃለሁኝ

ዘርህ እንደ አሸዋ በምድር ይበዛል

በአራቱም ማዕዘን ህዝብህም ይዘራል

አበው በምሳሌ እንደተናገሩት

ከምድር እስከ ሰማይ አምላክ የዘረጋው

በላይዋ ተቀምጦ በግልፅ የታየባት

የያዕቆብ መሰላል እመቤታችን ናት

ሰማይና ምድር የሚታረቁባት

ወልደ እገዋለ እምያው የተወለደባት

መላዕክት ከሰማይ በአንድ የዘመሩባት

ታካቋ መሰላል እመቤታችን ናት

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening