ጠቅላላ

General

አልፈርድም እኔ

Lyrics

አልፈርድም እኔ በማንም በደል በማንም ሃጢያት

በፈረድኩበት እንዳልመዘን ጌተ ሲመጣ በሃይል በስልጣን

በቸርነቱ አምላክ ባይተወው በደሌን ሁሉ

ውስጤ ቢፈተሽ በተሰጠኝ ህግ በቅዱስ ቃሉ

በምን ምግባሬ በሰው እፈርዳለሁ ዓይኔን አቅንቼ

በደሌ በዝቶ ለራሴ ሳላውቅ ለሃጢያት ሞቼ

ይልቅ የአንዱን ሸክም ሌላው ሰው አዝሎ መጓዝ ይችላል

መፍረድ ከመጣ አንድም ሰው አይድን ሁሉም በድሏል

ወንድም ወንድሙን እየከሰሰ ለፍርድ አቁሞ

አህዛብ ያያል በንትርኩ እጅግ ተገርሞ

ክርስትያን ሆኖ ከወንድሙ ጋር እየተጣላ

ዓለም ዳኘችን በጸብ ፍርድ ቤት ታረቁ ብላ

ክርስትያን ሆነን በአህዛብ መሃል እየተካሰስን

አምላክ አዘነ የመስቀሉን ዓላማ ትተን

መቼ ከሰሰ የከሰሱትን የገረፉትን

አይተናል እንጂ ለጠላቶቹ ምህረት ሲለምን

በጽድቅ ስራ ላይ ለእውነት ብለን መጥተናል እንጅ

ማን ነው የሾመን በወንድሞች ላይ አርጎ ፈራጅ

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening