✦
ጠቅላላ
•General
በጌቴ ሰማኔ
Lyrics
በጌቴሰማኔ በአታክልቱ ቦታ/2/
ለኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላታ /2/
አዳምና ሔዋን ባጠፉት ጥፋት /2/
እኛም ነበረብን የዘለዓለም ሞት /2/
መስቀል ተሸክሞ ሲወጣ ተራራ /2/
ይገርፉት ነበረ ሁሉም በየተራ /2/
በአምላክነቱ ሳይፈርድባቸው /2/
እንዲህ ሲል ጸለየ አባት ሆይ ማራቸው /2/
በረቂቅ ስልጣኑ ሁሉን የፈጠረ /2/
በሰው እጅ ተገርፎ ሞተ ተቀበረ /2/
ድንግል አልቻለችም እንባዋን ልትገታ /2/
እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ /2/
ፍቅሩን የገለጸው ተወልዶ በስጋ /2/
ኢየሱስ ክርስቶስ አልፋና ኦሜጋ /2/
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.