✦
ጠቅላላ
•General
የአብ ቃል አክብሮሽ
Lyrics
የአብ ቃል አክብሮሽ እናት ያደረገሽ
እግዚአብሔር በቃሉ ፍጹም ያከበረሽ
የምንመካብሽ መሰላል አንቺ ነሽ /2/
ቅድስና ለአንቺ ጽድቅም ለአንቺ ሆኖ
ዓለምን የፈጠረ በአንቺ ተወስኖ
የገነት ፍሬ ነሽ ሕይወትን ያፈራሽ
አንቺን ለመረጠ አንቺን ለአጸናሽ
ምስጋና ይድረሰው ለቸሩ አምላክሽ /2/
አዳም የኖረብሽ የኤዶም ገነት ነሽ
የኤፌሶን ወርቅ የሚፈልቅብሽ
የግዮን ማዕበል ኢትዮጵያን የከበብሽ
ዮርዳኖስ ሆነሽ አህዛብን ፈወስሽ
በልጁ ቃልነት አብም አከበረሽ /2/
መዓዛሽን ወዶ ወልድ ዋህድ ዋጀሽ
አብም በሰማያት በህሊናው ጻፈሽ
መንፈስ ቅዱስ መጥቶ አንቺን አከበረሽ
እመካብሻለሁ እመቤቴ ስልሽ /2/
ወልድ በመውደዱ ከአንቺ መወለዱን
ንጹህ ሆኖ አግኝቶሽ ቅዱሱን ስጋሽን
ለቃሉ ማደሪያው ጽላቱና ታቦት
በብሩህ ደመና ተመስለሽለት
ከስጋሽ ተከፍሎ ከደምሽ ደም ወሰዶ
ከነፍስሽም ነፍስ ፍጹም ተዋህዶ /4/
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.