ጠቅላላ

General

ተነሳልን

Lyrics

ተነሣልን መድኃኒታችን /2/

ከዲያቢሎስ ግዞት ነጻ ሊያወጣን

በመስቀል ተሰቅሎ ባፈሰሰው ደም

ተደመሰሰልን የሃጢአት መርገም

በጠንካራ ድንጋይ መቃብር ቢዘጋ /2/

ድል አድርጎ ተነሳ አልፋና ኦሜጋ /2/

ሞትን ድል አድርጎ ለተነሳው አምላክ

እኛን ከባርነት ለታደገን በእውነት

ጌታዬ ተመስገን ሌላ ምን እላለሁ /2/

ለከበረው ስምህ ምስጋና አቀርባለሁ /2/

እልልታን እናቅርብ ለሃያሉ ንጉሥ

ሞትን አጠፋልን እኛን ለመቀደስ

ከባርነት ቀንበር እኛን አላቆናል /2/

በመስቀል ተሰቅሎ ሕይወቱን ሰጥቶናል /2/

የአዳም ልጆች ሁሉ እንዘምር በእልልታ

ለሃያሉ እግዚአብሔር ለሰራዊት ጌታ

እንዘምር ዘምሩ ሰዎች ደስ ይበለን /2/

ሞትን አሳፍሮ ጌታ ተነሳልን /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening