ጠቅላላ

General

ዮርዳኖስ

Lyrics

ሐና እና ኢያቄም ወለዱ ሰማይ

አዲሷም ሰማይ አስገኘች ፀሐይ

ምስራቀ ምስራቃት የአምላክ መገኛ

ከሊባኖስ ድንግል ነይ ወደኛ(፪)

ተጨነቀ አዳም በመከራ

በእርግማን ቀን ለቅሶ እየዘራ

በልጅሽ ሞት ዓለም ተቀደሰ

የፍጥረቱ ዕንባ በመስቀል ታበሰ(፪)

የሕያዋን እናታቸው ሆነሽ

ለቀደመች ሔዋን ጠበቃ ሆንሽ

ደስተኛዋ ደስ ይበልሽ ማርያም

ከአንቺ ወጣ የዓለሙ ሰላም(፪)

ጽኑ ገመድ በአንቺ ተቆረጠ

የፍዳ ዓመት ይኸው ተለወጠ

በሐና ልጅ በኢያቄም ፍሬ

ደስታ ሆነ ቅኔ እና ዝማሬ(፪)

በወለዱሽ በሐና በኢያቄም

ተማጽነናል ድንግል ማርያም

ከአዳኝ ወጥመድ ከክፉ ጠላት

ልጆችሽን ጠብቂን ከጥፋት

ከአዳኝ ወጥመድ ከክፉ ጠላት

ኢትዮጵያን ጠብቂያት ከጥፋት

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening