✦
ጠቅላላ
•General
ዮርዳኖስ
Lyrics
ሐና እና ኢያቄም ወለዱ ሰማይ
አዲሷም ሰማይ አስገኘች ፀሐይ
ምስራቀ ምስራቃት የአምላክ መገኛ
ከሊባኖስ ድንግል ነይ ወደኛ(፪)
ተጨነቀ አዳም በመከራ
በእርግማን ቀን ለቅሶ እየዘራ
በልጅሽ ሞት ዓለም ተቀደሰ
የፍጥረቱ ዕንባ በመስቀል ታበሰ(፪)
የሕያዋን እናታቸው ሆነሽ
ለቀደመች ሔዋን ጠበቃ ሆንሽ
ደስተኛዋ ደስ ይበልሽ ማርያም
ከአንቺ ወጣ የዓለሙ ሰላም(፪)
ጽኑ ገመድ በአንቺ ተቆረጠ
የፍዳ ዓመት ይኸው ተለወጠ
በሐና ልጅ በኢያቄም ፍሬ
ደስታ ሆነ ቅኔ እና ዝማሬ(፪)
በወለዱሽ በሐና በኢያቄም
ተማጽነናል ድንግል ማርያም
ከአዳኝ ወጥመድ ከክፉ ጠላት
ልጆችሽን ጠብቂን ከጥፋት
ከአዳኝ ወጥመድ ከክፉ ጠላት
ኢትዮጵያን ጠብቂያት ከጥፋት
Ge'ez Translation / Meaning
የዮርዳኖስ ውኃ ከበረ ከሠማይ የሆነው በሰው እጅ በዩሐንስ ተጠመቀ
🙏 Help improve these lyrics
Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.