ጠቅላላ

General

የዓለምን በደል

Lyrics

የዓለምን በደል የሠውን ግፍ አይቶ

ዘጠና ዘጠኙን መላዕክቱን ትቶ

ፅድቅን ለመፈፀም በደልን አጥፍቶ

የሠላሙ መሪ የሠላሙ ዳኛ

አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለእኛ

የሰማዮች ሰማይ የማይችሉት ንጉሥ

ተወልዶ ሲጠመቅ እኛን ለመቀደስ

ተራሮች ደንግጠው ዘለሉ እንደፈረስ

ባህር ተጨነቀች ጠበባት መሬቱ

ዮርዳኖስም ሸሸ አልቆመም ከፊቱ

እንደተናገረው ዳዊት በትንቢቱ

ልጁ በዮርዳኖስ ፅድቅን ሲመሠርት

መጣ በደመና ሰማያዊው አባት

እየመሰከረ የልጁን ጌትነት

እንደምናነበው በወንጌል ተፅፎ

መንፈስ ቅዱስ ታየ በራሱ ላይ አርፎ

በርግብ ምሳሌ ክንፉን አሰይፎ

ባህር ስትጨነቅ ተራራው ሲጨፍር

ሰማዩ ሲከፈት ደመናው ሲናገር

ዓለም በዛሬው ቀን አየች ይህን ምስጢር

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening