ጠቅላላ

General

ጌታ ሆይ

Lyrics

ጌታ ሆይ አይሁድ አማፅያን ሰቀሉህ ወይ

የዓለም መድሀኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ወይ/2/

የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመሰቀል

የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት /2/

ንፁህ ክርስቶስ ሆንክ በደለኛ ብለህ ስለእኛ /2/

መስቀል አሸክመው አስረው ገረፋህ እያዳፋህ /2/

እጅና እግርህ በብረት ተመታ የዓለም ጌታ

የእሾህ አክሊል ደፍተህ ጐንህን ተወጋ

አልፋ ኦሜጋ /2/

ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው

ምራቅ እየተፋ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጐዱ/2/

በመስቀል ላይ ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል

ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው /2/

ይቅር ባይ ግልፅ በደላችን ሁሎ ሳታይ

አንተው ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening