ጠቅላላ

General

በእለተ ዓርብ

Lyrics

በእለተ ዓርብ ስላሴ ሰውን ፈጠሩ ለክብራቸው

የተፈጠሩትም አዳም ሔዋን ናቸው

በጠቅላላው ዓለም ሐይሉ ቢሰጣቸው

አፍርሰው ወደቁ በሰይጣን ተሳስተው

ወይ በደል ወይ ጉደት

የሁላችን አባት አዳም

ያን ጊዜ ጀመረ ለቅሶውን

ተሳስቶ በመብላት እፀ በለስን

ሊወስድ ፈልጐ አምላክነትን

ባልሆነ መካሪ በክፉ ሰይጣን

ወይ በደል ወይ ጉዳት

ከጐኔ ተፈጥረሽ ሄዋን

እንኳን ልትረጂኝ ጐደሺኝ

አንቺ ተሳስተሽ እኔን አሳትሺኝ

በማስመሰል ነግረሽ ስላበላሸኝ

እስከ መቼም ድረስ ሞቼ ቀረሁኝ

ወይ በደል ወይ ጉዳት

አተውቀሰኝ እንጂ አዳም

ምን ላድርግ ብለህ ነው ጌታዬ

ሰይጣን አስቶኝ ነው አዬ መከራዬ

እስከ መቼም ድረስ እሳት ነው ኑሮዬ

ስለተጣላሁኝ ከቸር ፈጣሪዬ

ወይ በደል ወይ ጉዳት

ያቺን ዕፀ በለስ ባትቆርጫት

ከሰይጣን ጋራ ተማክረሽ

የምድሩ ሳይበቃሽ የሰማይ ሽተሽ

እኔን አዋረድሺኝ አንቺም ተዋርደሽ

ከእንግዲህ ይጥቀምሽ ከንቱ ምኞትሽ

ወይ በደል ወይ ጉዳት

ያን ጊዜ ከገነት ሲወጡ

በእሳት ሲገፈፍ ክብራቸው

አንቺ ነሽ አንተ ነህ ሆነ ነገራቸው

ነገር ግን አየጠቅምም መነታሪካቸው

ወይ በደል ወይ ጉዳት

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening