ጠቅላላ

General

ክርስቶስ በስምህ

Lyrics

ክርስቶስ በስምህ ይዘናል ቀኖና

ስቅለት ትንሳኤህን እናያለን ገና

ጾም ማለት እንግዲህ ይሄ ነው ስርዓቱ

ሐዋርያት ጾመው ለኛ አበረከቱ

ነፈስና ስጋዬ በመብል ተጣለተው

ሽማግሌ ሆኖ ጾም አስታረቃቸው

አብረው እያደሩ አብረው እየዋሉ

አያምርም አይመስልም በመብል ሲጣሉ

ነፍስም ከስጋ ጋር መለየቷን አውቃ

የአለም ተድላዋን ደስታዋን ንቃ

በጾም በሱባኤ ትኖራለች ታጥቃ

ነፍስም ለስጋዋ ትመክረው ጀመረች

በብዙ ምሳሌ እያመሳሰለች

ስጋዬ ሞኝ ነህ መብልን አትውደደው

ከአዳም ጀምሮ ከመጀመሪያው ሰው

መብል ሲጐዳ እንዲ ሲጠቅም መች አየነው

🙏 Help improve these lyrics

Found a mistake or have a better version? Your contribution helps the community.

✍️ Contribute
🎵Select a Mezmur to begin listening